Telegram Group & Telegram Channel
እንደምን አላችሁ?
የነቢያት ጾም ሰንበታት የራሳቸው ስያሜዎች እንደ ዐቢይ ጾም ያላቸው ሲሆን የነገው ሰንበት ከጌታችን ፱ቱ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው ስያሜውም ስብከት ይባላል! 

ለነገው ቅዳሴ እንዲያግዝ የዕለቱ ግጻዌ ከነ ዝማሬው ከelam የቴሌግራም ገጽ  በክቡር አባታችን አባ ኃይለ ሚካኤል የተዘጋጀ  እናጋራችኋለን፤

መልካም በዓል


መዝሙር ዘስብከት ከታኅሣሥ ፯ - ፲፫

(በ፪/ዩ) ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ወልዶ መድኅነ ንሰብክ
ትርጕም፦
ቅድመ ዓለም የነበረ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን፤ የሰማዕታት አክሊል፣ ካህናትን የሚሾም፣ የመነኮሳት ተስፋ የሆነ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን።

የዕለቱ ምንባባት፦

ዕብ ፩፥፩ - ፍ፤
፪ጴጥ ፫፥፩ - ፲፤
ግብ ፫፥፲፯ - ፍ፤
የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፩፥፵፬ - ፍ፤
ቅዳሴ፦ ዘእግዚእነ

የዕለቱ ምስባክ፦
ፈኑ እዴከ እምአርያም፤
አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ፤
ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ ነኪር። መዝ ፻፵፫፥፯፤

ትርጉም፦

እጅህን ከአርያም ላክ፤
ከብዙ ውኃም አድነኝ፤
ከባዕድ ልጆችም አድነኝ።

ምሥጢር፦
ረድኤትህን ከአርያም ላክ አንድም ልጅህን በሥጋ ላክ፤
ከብዙ ጦር/ሠራዊት አድነኝ አንድም ከፍትወታት እኩያት ከኃጣውእ ርኩሳት ከፍዳ ከመከራ ነፍስ ፈጽመህ አድነኝ።
ከነናምሩድ ከነሳኦል ልጆች እጅ አድነኝ አንድም ከዲያብሎስ ወገኖች ሥልጣን አድነኝ።
ክንድ ከአካል ተገኝቶ ከአካል ሳይለይ ይኖራል፤ እሱም ከአብ ተገኝቶ ከአብ ሳይለይ ይኖራልና። ቦ የሰው ኃይሉ በክንዱ እንዲታወቅ የአብም ኃይሉ በወልድ ታውቋልና። ቦ ክንድ ከአካል ሳይለይ የወደቀ አንሥቶ ይመለሳል፤ እሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አንድነት ሳይለይ የወደቀ አዳምን አንሥቶ ተመልሷልና። ቦ በክንድ የራቀ ያቀርቡበታል የቀረበ ያርቁበታል፤ የራቀ አዳምን አቅርቦበታል የቀረበ ዲያብሎስን አርቆበታልና። ቦ በክንድ አሥረው ያጠብቁበታል ወርውረው ያርቁበታል፤ ዲያብሎስን በእሳት ዛንጅር ይዞ በነፋስ አውታር አሥሮ ከሰው ሕይወት አርቆበታልና። ቦ በክንድ የታሠረ ይፈቱበታል የተፈታ ያሥሩበታል፤ የታሠረ አዳምን ፈትቶበታል የተፈታ ዲያብሎስን አሥሮበታልና። ኋላም ሑሩ እምኔየ ብሎ ያርቅበታል ንዑ ኀቤየ ብሎ ያቀርብበታልና እጅህን ላክ አለ።
መልእክት፦
ዛፍ ከሥሩ ሳይነቀል ጫፉ መሬት ነክቶ ይመለሳል የአምላክ ሰው የመሆን ምሥጢርም እንዲሁ ነው። ምሥጢሩ የዚህን ያህል ጥልቅና ረቂቅ ከሆነ በምሥጢረ ሥጋዌ ዙሪያ አምላክ እንዴት ሰው እንደሆነ ሰውም እንዴት አምላክ እንደሆነ ተመራምሬ እደርሳለሁ ማለት የውቅያኖስን ውኃ በእንቁላል ቅርፊት ቀድቶ ለመጨረስ እንደመሞከር ነው።

©



tg-me.com/orthodox1/12830
Create:
Last Update:

እንደምን አላችሁ?
የነቢያት ጾም ሰንበታት የራሳቸው ስያሜዎች እንደ ዐቢይ ጾም ያላቸው ሲሆን የነገው ሰንበት ከጌታችን ፱ቱ ንዑሳን በዓላት አንዱ ነው ስያሜውም ስብከት ይባላል! 

ለነገው ቅዳሴ እንዲያግዝ የዕለቱ ግጻዌ ከነ ዝማሬው ከelam የቴሌግራም ገጽ  በክቡር አባታችን አባ ኃይለ ሚካኤል የተዘጋጀ  እናጋራችኋለን፤

መልካም በዓል


መዝሙር ዘስብከት ከታኅሣሥ ፯ - ፲፫

(በ፪/ዩ) ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ወልዶ መድኅነ ንሰብክ
ትርጕም፦
ቅድመ ዓለም የነበረ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን፤ የሰማዕታት አክሊል፣ ካህናትን የሚሾም፣ የመነኮሳት ተስፋ የሆነ መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን።

የዕለቱ ምንባባት፦

ዕብ ፩፥፩ - ፍ፤
፪ጴጥ ፫፥፩ - ፲፤
ግብ ፫፥፲፯ - ፍ፤
የዕለቱ ወንጌል፦ ዮሐ ፩፥፵፬ - ፍ፤
ቅዳሴ፦ ዘእግዚእነ

የዕለቱ ምስባክ፦
ፈኑ እዴከ እምአርያም፤
አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ፤
ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ ነኪር። መዝ ፻፵፫፥፯፤

ትርጉም፦

እጅህን ከአርያም ላክ፤
ከብዙ ውኃም አድነኝ፤
ከባዕድ ልጆችም አድነኝ።

ምሥጢር፦
ረድኤትህን ከአርያም ላክ አንድም ልጅህን በሥጋ ላክ፤
ከብዙ ጦር/ሠራዊት አድነኝ አንድም ከፍትወታት እኩያት ከኃጣውእ ርኩሳት ከፍዳ ከመከራ ነፍስ ፈጽመህ አድነኝ።
ከነናምሩድ ከነሳኦል ልጆች እጅ አድነኝ አንድም ከዲያብሎስ ወገኖች ሥልጣን አድነኝ።
ክንድ ከአካል ተገኝቶ ከአካል ሳይለይ ይኖራል፤ እሱም ከአብ ተገኝቶ ከአብ ሳይለይ ይኖራልና። ቦ የሰው ኃይሉ በክንዱ እንዲታወቅ የአብም ኃይሉ በወልድ ታውቋልና። ቦ ክንድ ከአካል ሳይለይ የወደቀ አንሥቶ ይመለሳል፤ እሱም ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ አንድነት ሳይለይ የወደቀ አዳምን አንሥቶ ተመልሷልና። ቦ በክንድ የራቀ ያቀርቡበታል የቀረበ ያርቁበታል፤ የራቀ አዳምን አቅርቦበታል የቀረበ ዲያብሎስን አርቆበታልና። ቦ በክንድ አሥረው ያጠብቁበታል ወርውረው ያርቁበታል፤ ዲያብሎስን በእሳት ዛንጅር ይዞ በነፋስ አውታር አሥሮ ከሰው ሕይወት አርቆበታልና። ቦ በክንድ የታሠረ ይፈቱበታል የተፈታ ያሥሩበታል፤ የታሠረ አዳምን ፈትቶበታል የተፈታ ዲያብሎስን አሥሮበታልና። ኋላም ሑሩ እምኔየ ብሎ ያርቅበታል ንዑ ኀቤየ ብሎ ያቀርብበታልና እጅህን ላክ አለ።
መልእክት፦
ዛፍ ከሥሩ ሳይነቀል ጫፉ መሬት ነክቶ ይመለሳል የአምላክ ሰው የመሆን ምሥጢርም እንዲሁ ነው። ምሥጢሩ የዚህን ያህል ጥልቅና ረቂቅ ከሆነ በምሥጢረ ሥጋዌ ዙሪያ አምላክ እንዴት ሰው እንደሆነ ሰውም እንዴት አምላክ እንደሆነ ተመራምሬ እደርሳለሁ ማለት የውቅያኖስን ውኃ በእንቁላል ቅርፊት ቀድቶ ለመጨረስ እንደመሞከር ነው።

©

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/12830

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

What is Telegram Possible Future Strategies?

Cryptoassets enthusiasts use this application for their trade activities, and they may make donations for this cause.If somehow Telegram do run out of money to sustain themselves they will probably introduce some features that will not hinder the rudimentary principle of Telegram but provide users with enhanced and enriched experience. This could be similar to features where characters can be customized in a game which directly do not affect the in-game strategies but add to the experience.

Telegram hopes to raise $1bn with a convertible bond private placement

The super secure UAE-based Telegram messenger service, developed by Russian-born software icon Pavel Durov, is looking to raise $1bn through a bond placement to a limited number of investors from Russia, Europe, Asia and the Middle East, the Kommersant daily reported citing unnamed sources on February 18, 2021.The issue reportedly comprises exchange bonds that could be converted into equity in the messaging service that is currently 100% owned by Durov and his brother Nikolai.Kommersant reports that the price of the conversion would be at a 10% discount to a potential IPO should it happen within five years.The minimum bond placement is said to be set at $50mn, but could be lowered to $10mn. Five-year bonds could carry an annual coupon of 7-8%.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from kr


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA